Skip to main content

Posts

Showing posts from May, 2024

በፌደራል ጥብቅና አገልግሎት ፍቃድ አሰጣጥ እና አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1249/2014 አንዳንድ ድንጋጌዎች ላይ የቀረበ አጭር የመነሻ ሃሳብ ጽሁፍ

     በጠበቃ ዘርኣይ ወልደሰንበት 1. የፌደራል ጥብቅና አገልግሎት ፍቃድ አሰጣጥ እና አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1249/2014 አንቀጽ 63(11) ድንጋጌ መሠረት የማህበሩ ጠቅላላ ጉባዔ ሥልጣን የተሰጠው የማኅበሩን መተዳደሪያ ደንብ የማውጣት ሥልጣን ነው? ወይንስ የማኅበሩን መመስረቻ ጽሁፍ የማውጣት ሥልጣን ነው? Article 63(11) of Federal Advocacy Service Licensing and Administration Proclamation No. 1249/2021 stipulated that the General Meeting shall have the power and duty to "Issue the Memorandum of Association of the Association amend and approve same." while its Amharic counterpart says that የማህበሩ ጠቅላላ ጉባዔ "የማኅበሩን መተዳደሪያ ደንብ ያወጣል፣ ያሻሽላል፣ ያጸድቃል፡፡" በማለት ደንግጓል፡፡  በዚህም መሠረት በፌደራል ጥብቅና አገልግሎት ፍቃድ አሰጣጥ እና አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1249/2014 አንቀጽ 63(11) ድንጋጌ የእንግሊዝኛው ቅጂ ላይ የማህበሩ ጠቅላላ ጉባኤ የማኅበሩን መመስረቻ ጽሁፍ ያወጣል በሚል በግልጽ የተደነገገ ሲሆን የዚሁ አንቀጽ ድንጋጌ የአማርኛ ቅጂ በበኩሉ ደግሞ የማህበሩ ጠቅላላ ጉባኤ የማኅበሩን መተዳደሪያ ደንብ ያወጣል፡፡" በሚል በግልጽ ተደንግጓል፡፡ ከዚህም አንጻር፣ በአዋጁ አንቀጽ 63(11) ድንጋጌ የአማርኛ እና የእንግሊዝኛ ቅጂዎች መካከል ግልጽ የሆነ መሰረታዊ ልዩነት ይገኛል፡፡ እንዲህ ያሉ አጋጣሚዎች በሚያጋጥሙበት ጊዜ የሕግ አውጪው ትክክለኛ ሀሳብና ፍላጎት ምንም ይሁን ምን የአማርኛው ቅጂ ተፈጻሚነት ይኖረዋል ...