Skip to main content

Posts

Showing posts with the label Court of Law

“መዝገቡ አያሳይም!”

  በፍርድ ቤት የሚደረጉ ክርሮች እና የሚሰሙ ምሥክሮች በተለይ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመቅረፀ ድምፅ ይያዛሉ፡፡ በፌዴራል የመጀመሪያ ፍርድ ቤቶች ግን አብዛኖቹ ክርከሮች እና የምስክሮች ቃል በዳኞች በእጅ ይፃፋል፡፡ በእነዚህ ችሎቶች ምሥክሮቻችሁ ያስረዱላችሁ ጭብጦች ሳይመዘገብላችሁ ቀርቶ ያውቃል? በመስቀለኛ ጥያቄያችሁ ያስጣላችሁት ነጥብ በፍርድ ቤት መዝገብ ውስጥ ሽታው ጠፍቶባችሁ ያውቅ ይሆን? በስር ፍርድ ቤት በምሥክሮች ስለመነገሩ እርግጠኛ የሆናችሁበትን ፍሬ ነገር ተመስርታችሁ ይግባኝ ጠይቃችሁ በይግባኝ ችሎቱ “እርሶ በምሥክሮች ተነግሯል ቢሉም ከስር ፍርድ ቤት መዝገብ የሚሉትን አያሳይም” ተብላችሁ ኩም ብላችሁ ታውቃላችሁ? እኔን ገጥሞኝ ያውቃል! ግን ለምን??? አንድ ጠበቃ ወዳጄ የገጠማትን አጫወተችኝ፡፡ በፍርድ ቤት መድረክ ግራ ቀኙ ምስክሮቻቸውን አቅርበው እየተፋለሙ ነው፡፡ የምተርከው ገጠመኝ የተፈጠረው የወዳጄ ባላጋራዎች   ምሥክር ቀርቦ በሚሰማበት ወቅት ነው፡፡ ምሥክሩ ባቀረበው ጠበቃ   ሲጠየቅ ቆይቷል፡፡ ምሥክሩን ያቀረበው ጠበቃ የሚጠይቀው የጥያቄ ዓይነት ዋና ጥያቄ ይባላል፤ በዋና ጥያቄ የሚቀርቡት ጥያቄዎች ምስክሩ የሚያስረዳውን ጉዳይ የመንገር ያህል እንዲሆኑ አይፈቀዱም፤ መሰል ጥያቄዎች መሪ ጥያቄ ይባላሉ፡፡ በተቃራኒው ደንበኛውን ወክሎ ምሥክሩን ያቀረበው ጠበቃ ዋና ጥያቄ አቅርቦ እንደጨረሰ ባላንጣው ጠበቃ የምስክሩን ቃል ተዓማኒነት ለማሳጣት ወይም ለማፍረስ ይጠይቃል፤ ይህ የጥያቄ ዓይነት መስቀለኛ ጥያቄ መጠሪያው ነው፡፡ በመስቀለኛ ጥያቄ ወቅት ምሥክሩን ያቀረበው ጠበቃ ከጠየቃቸው ወይም ምሥክሩ ካብራራው ርዕሰ ጉዳዮች ወይም ከእነዚህ ርዕሰ ጉዳዮች ጋር በቀጥታ ከሚገናኙ ፍሬ ነገሮች ውጪ መጠየቅ አ...

Judicial Bias by the Judge For Recusal of a Judge in Ethiopia

   By: Zeray Weldesenbet   The overall objective of this short legal note is to provide highlights on the meaning of the provision of Article 33(1)(e) of Federal Courts Proclamation No. 1234/2021, raises important considerations regarding judicial bias, and emphasizes the importance of considering judicial bias and its implications for seeking the recusal of a judge.   "A judge of a federal court shall be removed from his bench where there are sufficient reasons, other than those specified under sub-article (1)(a) to (1)(d) of article 33, to conclude that injustice may be done.“, according to Article 33(1)(e) of the Federal Courts Proclamation No. 1234/2021.   And what are the possible circumstances or reasons that could fall within this specific legal provision? Can judicial bias fall within this ambit of the legal provision at hand? If so, what factors indicate bias against one party of a case by the judge?   Proving judicial bias or prej...

የፍትህ ሥርዓቱ ግብ ፍትህ ሣይሆን ሕግ እና ሥርዓት (law and order) ነው!

የፍትህ ሥርዓቱ ግብ ፍትህ ሣይሆን ሕግ እና ሥርዓት ነው የምለው ደስ እያለኝ ሳይሆን እያዘንኩ ነው፡፡ ይህን ጉዳይ ይበልጡን ባሰብኩት ቁጥር ፍትህ በሰው ልጅ እጅ አለፍ አለፍ እያለች ያጋጣሚ ልትገኝ ትችል ይሆናል እንጂ ትክክለኛ ፍትህ መስጠት ልዕለ ሰብ ሃይል ጣልቃ ገብነት ይፈልጋል፡፡ በሕግ ሞያ ባለሟልነት መስራት የራሱ ፈተናዎች፣ የራሱ ግራመጋባቶች (confusion and dilemma) አለው፡፡ አንዳንዴ የሕግ ሞያዬ ከሰው ልጅ ሁሉ ጋር በጅምላ ያጣላኛል፤ ፀቤ የማይታይ ነው፤ ልቦናዬ ውስጥ ነው፡፡ ሌላ ጊዜ ደግሞ ፀቤ ከራሴ ጋር ይሆናል፡፡ አንድ የህግ ባለሞያ በፍትህ ሥርዓቱ ውስጥ ያለውን ሚና ለመወጣት በሚያደርገው ጥረት ከራሱም ጋር ሳይቀር ይጣላል፡፡ ዳኛ፣ ጠበቃ፣ ነገረፈጅ ወይም ዐቃቤ ሕግ ሆኖ የተሰጠውን ሚና ለመወጣት ሲባትል ከራሴ ጋር ተጣልቼ አላውቅም የሚል ካለ ወይ ህሊናው መጅ አውጥቷል ካልሆነም የሰው ልጅ ድክመት ያልተጣባው የፍትህ ሥርዓቱን በተአምር የሚዘውር መልአክ ወይም ልቦናው ማመዛዘኑን የተነጠቀ አጋንንት ነው ስል መሞገቴ አይቀርም፡፡ ያለፈው ሰሞን አንድ ችሎት ውስጥ ነበርኩ፡፡ የተረጋጋ ባለጉዳዮችን በአክብሮት የሚያስተናግድ ሰብአዊነቱን በቀላሉ ልገነዘብለት የቻልኩት ዳኛ ተሰይሟል፡፡ ሦስት ጠበቆች እና አንድ ዐቃቤ ህግ ከፊቱ ቆመው ሙሉ ሰዓት ሊሞላ ጥቂት ለቀራቸው ደቂቃዎች የወከሉትን ወገን ፅድቅ ሲያገዝፉ የሌላኛውን ወገን ኃጢያት ሲያገኑ ቆዩ፡፡  ጉዳዩ የመኖሪያ ቤትን የተመለከተ የፍትሃብሄር ጉዳይ ነው፡፡ በክርክሩ ሂደት ከሣሽ የሆኑት ባልቴት ከጠበቃቸው ጀርባ ተቀምጠው፣ ወደ ምድር አቀርቅረው ድምፅ ሳያወጡ ያነበንባሉ፡፡ ፀሎት መስሎኝ ነበር፡፡ በኋላ ግን ደረቅ ፀሎት ሳይሆን በእንባ የረሰረሰ ምልጃ እንደሆነ ታዘብኩ፡፡ እኔም ተራዬ...