Skip to main content

Posts

Showing posts with the label law of succession

ሸሽተው የማያመልጡት፣ ውርስ

  “ሰው ከተወለደበት ቀን አንስቶ እስከ ሞተበት ቀን ድረስ የህግ መብት አለው፡፡” የፍትሃ ብሄር ህግ ቁጥር 1 አምስት መፅሃፍትን፣ 3367 ድንጋጌዎችን አካቷል፣ ሚያዚያ 27 ቀን 1952 ዓ.ም ታውጆ ከመስከረም 1 ቀን 1953 ጀምሮ ተፈፃሚ የተደረገው አብዛኛው ክፍሉ አሁንም ተፈፃሚ የሆነው የፍትሃ ብሄር ህጋችን በርካታ ህጎችን ያቀፈ የህጎች ስብስብ ነው፡፡ በውስጡ ከያዛቸው መካከል የውርስ ወይም የአወራረስ ህግ ይገኛል፡፡ በሁለተኛው መፅሃፍ አንቀፅ አምስት ውስጥ ከቁጥር 826 እስከ 1125 ድረስ ያሉት 299 ቁጥሮች የውርስ ጉዳይን የሚደነግጉ ናቸው፡፡   ውርስ ማናችንንም ሊያጋጥመን   የሚችል ጉዳይ ነው፡፡ የውርስ ህግ ክፍል ባይሆንም ውርስ የተሰኘው ፅንሰ ሃሳብ እንዲኖር መግቢያዮ ላይ ያሰፈርኩት ድንጋጌ ትልቅ ቦታ አለው፡፡ ለዚህ ነው ብዙ ጊዜ የሃገራችን የህግ ምሁራን የውርስ ህግን ለማብራራት ሲነሱ ከዚህ ቀጥር የሚጀምሩት፡፡ የትኛውም ሰው ከተወለደበት ቀን ጀምሮ ባለመብት ነው፡፡ በተለያየ መልኩ የተለያዩ መብቶች እና ግዴታዎች ይኖሩታል፡፡ ሃገራችን የተቀበለቻቸው የተለያዩ ዓለም አቀፍ ህግጋትም መብቶችን ይሰጡታል፡፡ ከእነዚህም መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል፡-   UDHR (UNIVERSAL DECLARATION OF HUMAN RIGHTS) Article 17 1.    Everyone has the right to own property alone as well as in association with others.     በዚህ ድንጋጌ መሰረት የትኛውም ሰው ከሌሎችም ጋር ሆነ ለብቻው የራሱ ንብረት የማፍራት መብት አለው፡፡ ግን ንብረቱ ከየት ይመጣል? መልሱን ICESCR (INTERNATI...

ገድሎ መውረስ ይቻል ይሆን? (Is Killing to Inherit possible?)

  “No one shall be permitted to profit by his own fraud, or to take advantage of his own wrong, or to found any claim up on iniquity, or to acquire property by his own crime.”                      Riggs v palmer, New York court (1889) የጥንት ታሪክ ነው፤ግን በጣም ታዋቂ ታሪክ ነው፡፡ አሜሪካ ኒው ዮርክ ከተማ ውስጥ በ1882 (በእነሱው አቆጣጠር)ነው፡፡ ኤልመር የተባለ ግለሰብ አያቱን ገደላቸው፤ካለምንም ርእራሄ ምስኪኑን ሽማግሌ በመርዝ ገደላቸው፡፡ አያትየው ከዘመዶቻቸው ሁሉ የሚወዱት የልጅ ልጃቸው ነው መሰል አብዛኛውን ንብረታቸውን ለአቶ ኤልመር ነው የተናዘዙት፡፡አያቱ እስኪሞቱ መጠበቅ ሰልችቶት አይደለም የገደላቸው፤ተቀናቃኝ መጥቶበት እንጂ፡፡ እርጅና አጋርን መፈለግን እና ፍቅርን አይከለክልምና አያቱ ሚስት አገቡ፡፡ ልላ ተቀናቃኝ ተወዳጅ ሰው መምጣቱን ያስተዋለው ኤልመን የቀድሞውን ኑዛዜ አያቱ እንዳይቀይሩት ሰጋ፡፡ አሰበ፤ተጨነቀ፤ልያጣው የሜችለው ሃብት አይኑን አቀላው፤አንገበገበው፤አስገበገበው፡፡ አያቱን በመርዝ ገደላቸው፤ኑዛዜውን ሳይቀይሩ ሳይቀደም መቅደሙ ነው፡፡ለነገሩ እኮ ሰውየው ጭራሽ ኑዛዜያቸውንም ላይለውጡት ይችሉ ነበር፡፡   ከብዙ ምርመራና ክትትል በኋላ በድብቅ የሰራው ወንጀል ፀሃይ ሞቀው እና የኤልመር ወንጀል ተደረሰበት፤ፍርድ ቤት ቀረበ ከዛም ተፈረደበት፡፡አመታትንም በእስር ቤት አሳለፈ፤ፍርዱን ሲጨርስም ከእስር ተለቀቀ፡፡ይሄኔ አቶ ኤልመር...