“ሰው ከተወለደበት ቀን አንስቶ እስከ ሞተበት ቀን ድረስ የህግ መብት አለው፡፡” የፍትሃ ብሄር ህግ ቁጥር 1 አምስት መፅሃፍትን፣ 3367 ድንጋጌዎችን አካቷል፣ ሚያዚያ 27 ቀን 1952 ዓ.ም ታውጆ ከመስከረም 1 ቀን 1953 ጀምሮ ተፈፃሚ የተደረገው አብዛኛው ክፍሉ አሁንም ተፈፃሚ የሆነው የፍትሃ ብሄር ህጋችን በርካታ ህጎችን ያቀፈ የህጎች ስብስብ ነው፡፡ በውስጡ ከያዛቸው መካከል የውርስ ወይም የአወራረስ ህግ ይገኛል፡፡ በሁለተኛው መፅሃፍ አንቀፅ አምስት ውስጥ ከቁጥር 826 እስከ 1125 ድረስ ያሉት 299 ቁጥሮች የውርስ ጉዳይን የሚደነግጉ ናቸው፡፡ ውርስ ማናችንንም ሊያጋጥመን የሚችል ጉዳይ ነው፡፡ የውርስ ህግ ክፍል ባይሆንም ውርስ የተሰኘው ፅንሰ ሃሳብ እንዲኖር መግቢያዮ ላይ ያሰፈርኩት ድንጋጌ ትልቅ ቦታ አለው፡፡ ለዚህ ነው ብዙ ጊዜ የሃገራችን የህግ ምሁራን የውርስ ህግን ለማብራራት ሲነሱ ከዚህ ቀጥር የሚጀምሩት፡፡ የትኛውም ሰው ከተወለደበት ቀን ጀምሮ ባለመብት ነው፡፡ በተለያየ መልኩ የተለያዩ መብቶች እና ግዴታዎች ይኖሩታል፡፡ ሃገራችን የተቀበለቻቸው የተለያዩ ዓለም አቀፍ ህግጋትም መብቶችን ይሰጡታል፡፡ ከእነዚህም መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል፡- UDHR (UNIVERSAL DECLARATION OF HUMAN RIGHTS) Article 17 1. Everyone has the right to own property alone as well as in association with others. በዚህ ድንጋጌ መሰረት የትኛውም ሰው ከሌሎችም ጋር ሆነ ለብቻው የራሱ ንብረት የማፍራት መብት አለው፡፡ ግን ንብረቱ ከየት ይመጣል? መልሱን ICESCR (INTERNATI...
Legathiopia is a bilingual blog that documents the learning journey of a practicing attorney and host of the Legal Plus podcast. The blog features articles in both English and Amharic, focusing on the Ethiopian legal system and related fields. It serves as a platform for professional discourse, scholarly opinions, and intellectual analysis, aiming to enhance understanding of Ethiopia's legal environment.