Skip to main content

Posts

Judicial Bias by the Judge For Recusal of a Judge in Ethiopia

   By: Zeray Weldesenbet   The overall objective of this short legal note is to provide highlights on the meaning of the provision of Article 33(1)(e) of Federal Courts Proclamation No. 1234/2021, raises important considerations regarding judicial bias, and emphasizes the importance of considering judicial bias and its implications for seeking the recusal of a judge.   "A judge of a federal court shall be removed from his bench where there are sufficient reasons, other than those specified under sub-article (1)(a) to (1)(d) of article 33, to conclude that injustice may be done.“, according to Article 33(1)(e) of the Federal Courts Proclamation No. 1234/2021.   And what are the possible circumstances or reasons that could fall within this specific legal provision? Can judicial bias fall within this ambit of the legal provision at hand? If so, what factors indicate bias against one party of a case by the judge?   Proving judicial bias or prej...

በፌደራል ጥብቅና አገልግሎት ፍቃድ አሰጣጥ እና አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1249/2014 አንዳንድ ድንጋጌዎች ላይ የቀረበ አጭር የመነሻ ሃሳብ ጽሁፍ

     በጠበቃ ዘርኣይ ወልደሰንበት 1. የፌደራል ጥብቅና አገልግሎት ፍቃድ አሰጣጥ እና አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1249/2014 አንቀጽ 63(11) ድንጋጌ መሠረት የማህበሩ ጠቅላላ ጉባዔ ሥልጣን የተሰጠው የማኅበሩን መተዳደሪያ ደንብ የማውጣት ሥልጣን ነው? ወይንስ የማኅበሩን መመስረቻ ጽሁፍ የማውጣት ሥልጣን ነው? Article 63(11) of Federal Advocacy Service Licensing and Administration Proclamation No. 1249/2021 stipulated that the General Meeting shall have the power and duty to "Issue the Memorandum of Association of the Association amend and approve same." while its Amharic counterpart says that የማህበሩ ጠቅላላ ጉባዔ "የማኅበሩን መተዳደሪያ ደንብ ያወጣል፣ ያሻሽላል፣ ያጸድቃል፡፡" በማለት ደንግጓል፡፡  በዚህም መሠረት በፌደራል ጥብቅና አገልግሎት ፍቃድ አሰጣጥ እና አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1249/2014 አንቀጽ 63(11) ድንጋጌ የእንግሊዝኛው ቅጂ ላይ የማህበሩ ጠቅላላ ጉባኤ የማኅበሩን መመስረቻ ጽሁፍ ያወጣል በሚል በግልጽ የተደነገገ ሲሆን የዚሁ አንቀጽ ድንጋጌ የአማርኛ ቅጂ በበኩሉ ደግሞ የማህበሩ ጠቅላላ ጉባኤ የማኅበሩን መተዳደሪያ ደንብ ያወጣል፡፡" በሚል በግልጽ ተደንግጓል፡፡ ከዚህም አንጻር፣ በአዋጁ አንቀጽ 63(11) ድንጋጌ የአማርኛ እና የእንግሊዝኛ ቅጂዎች መካከል ግልጽ የሆነ መሰረታዊ ልዩነት ይገኛል፡፡ እንዲህ ያሉ አጋጣሚዎች በሚያጋጥሙበት ጊዜ የሕግ አውጪው ትክክለኛ ሀሳብና ፍላጎት ምንም ይሁን ምን የአማርኛው ቅጂ ተፈጻሚነት ይኖረዋል ...

የፍትህ ሥርዓቱ ግብ ፍትህ ሣይሆን ሕግ እና ሥርዓት (law and order) ነው!

የፍትህ ሥርዓቱ ግብ ፍትህ ሣይሆን ሕግ እና ሥርዓት ነው የምለው ደስ እያለኝ ሳይሆን እያዘንኩ ነው፡፡ ይህን ጉዳይ ይበልጡን ባሰብኩት ቁጥር ፍትህ በሰው ልጅ እጅ አለፍ አለፍ እያለች ያጋጣሚ ልትገኝ ትችል ይሆናል እንጂ ትክክለኛ ፍትህ መስጠት ልዕለ ሰብ ሃይል ጣልቃ ገብነት ይፈልጋል፡፡ በሕግ ሞያ ባለሟልነት መስራት የራሱ ፈተናዎች፣ የራሱ ግራመጋባቶች (confusion and dilemma) አለው፡፡ አንዳንዴ የሕግ ሞያዬ ከሰው ልጅ ሁሉ ጋር በጅምላ ያጣላኛል፤ ፀቤ የማይታይ ነው፤ ልቦናዬ ውስጥ ነው፡፡ ሌላ ጊዜ ደግሞ ፀቤ ከራሴ ጋር ይሆናል፡፡ አንድ የህግ ባለሞያ በፍትህ ሥርዓቱ ውስጥ ያለውን ሚና ለመወጣት በሚያደርገው ጥረት ከራሱም ጋር ሳይቀር ይጣላል፡፡ ዳኛ፣ ጠበቃ፣ ነገረፈጅ ወይም ዐቃቤ ሕግ ሆኖ የተሰጠውን ሚና ለመወጣት ሲባትል ከራሴ ጋር ተጣልቼ አላውቅም የሚል ካለ ወይ ህሊናው መጅ አውጥቷል ካልሆነም የሰው ልጅ ድክመት ያልተጣባው የፍትህ ሥርዓቱን በተአምር የሚዘውር መልአክ ወይም ልቦናው ማመዛዘኑን የተነጠቀ አጋንንት ነው ስል መሞገቴ አይቀርም፡፡ ያለፈው ሰሞን አንድ ችሎት ውስጥ ነበርኩ፡፡ የተረጋጋ ባለጉዳዮችን በአክብሮት የሚያስተናግድ ሰብአዊነቱን በቀላሉ ልገነዘብለት የቻልኩት ዳኛ ተሰይሟል፡፡ ሦስት ጠበቆች እና አንድ ዐቃቤ ህግ ከፊቱ ቆመው ሙሉ ሰዓት ሊሞላ ጥቂት ለቀራቸው ደቂቃዎች የወከሉትን ወገን ፅድቅ ሲያገዝፉ የሌላኛውን ወገን ኃጢያት ሲያገኑ ቆዩ፡፡  ጉዳዩ የመኖሪያ ቤትን የተመለከተ የፍትሃብሄር ጉዳይ ነው፡፡ በክርክሩ ሂደት ከሣሽ የሆኑት ባልቴት ከጠበቃቸው ጀርባ ተቀምጠው፣ ወደ ምድር አቀርቅረው ድምፅ ሳያወጡ ያነበንባሉ፡፡ ፀሎት መስሎኝ ነበር፡፡ በኋላ ግን ደረቅ ፀሎት ሳይሆን በእንባ የረሰረሰ ምልጃ እንደሆነ ታዘብኩ፡፡ እኔም ተራዬ...