ረሃብ ክፉ ነው፡፡ ረሃብ አንጀትን ብቻ አይደለም የሚያጥፈው፡፡ አንገትን ያሳጥፋል፣ አስደፍቶ፡፡ ወዝን ያጠፋል፡፡ ግርማ ሞገስን ይነጥቃል፡፡ ረሃብ ክፉ ነው፡፡ ሰውየው የዚሁ የክፉው ረሃብ ምርኮኛ፣ የረሃብ ሰንሰለት እስረኛ ናቸው፡፡ ረሃብ አንጀታቸውን ብቻ አይደለም ያጠፉት አንገታቸውን ጭምር እንጂ፡፡ ግርማ ሞገሳቸውን ነጥቆ፣ ወዛቸውን መጦ ‹‹ረሃብተኛ›› አርጓቸዋል፡፡ ታዲያ ሌላ ምን ይባላላል፤ ረሃብ ስማቸውን ቀምቶ ‹‹ረሃብተኛ››፣ ‹‹ችግረኛ›› ወይም ፈረንጆቹ እንደሚሉት ‹ሆምለስ› (homeless) የተሰኙ አዳዲስ ስሞች አሰጣቸው፡፡ ይህ ሰው ኑሮ የተጫናቸውን፣ የሚቀምሱት ያጡትን ሁሉ ለማመልከት የተፈጠረ ተምሳሌታዊ ሰው አይደለም፡፡ አቶ ኦስትሪያቮቭ ተብሎ የሚጠራ ዩክሬናዊ ደም ያለው ጣልያን ውስጥ የሚኖር ነዳይ ነው፡፡ ታሪኩን የዘገበው ቢቢሲ ምን ያህል ቀናት ካለምግብ ያለፈቃዱ እንደፆመ ባይነግረንም መራብ ግን ተርቧል፡፡ እናም የታጠፈ አንጀቱን ለማላወስ ወደ አንዱ ሱፐርማርኬት ገባ እና ዳቦ፣ ሁለት ፍሬ አይብ እና የታሸገ ስጎ አንስቶ ለዳቦው ብቻ ከፍሎ ሊወጣ ሲል ጉዳዩን ሲያስተውል የነበረ ሌላ ተጠቃሚ ለጥበቃዎች አሰታውቆ አስያዘው፡፡ ሳይከፍል ይዞት ሊወጣ የነበረው ቺዝ እና ስጎ 4.50 የሜሪካ ዶላር ዋጋ ያለው ነው፤ በኢትዮጵያ ገንዘብ ብር ማለት ነው፡፡ እናም በፖሊስ እጅ ወደቀ፤ በ2011 እንደ ምዕራባውያን አቆጣጠር፡፡ በ2015 ዓ.ም (አሁንም በምዕራባውያን አቆጣጠር) ፍርድ ቤቱ (ለዚህች ጉዳይ እስከዛ የማንን ጎፈሬ ሲያበጥር እንደነበር እንጃ) ጥፋተኛ ብሎ ስድስት ወር እስራት እና 100 ይሮ የገንዘብ ቅጣት ወሰነበት፡፡ ርቦት የሰረቀ የመጀመሪያው ሰው አይደለም፡፡ እግዲያውስ የሱን...
Legathiopia is a bilingual blog that documents the learning journey of a practicing attorney and host of the Legal Plus podcast. The blog features articles in both English and Amharic, focusing on the Ethiopian legal system and related fields. It serves as a platform for professional discourse, scholarly opinions, and intellectual analysis, aiming to enhance understanding of Ethiopia's legal environment.